Saturday, May 12, 2012

http:///? www.meleket4u.blogspot.com/

Thursday, May 10, 2012


ማን አሸነፈ?

በቤተክርስቲያን አሸናፊ አይኖርም ብሎ መረዋ የጻፈው ከ ፫ ዓመት በፊት ነበር። መረዋ ዛሬም ማንም አሸናፊ አይደለም ብሎ ያምናል። እንዴውም የገደለው ባሌ የሞተው ወንድሜ የሚለውንም እንደ ምሳሌ መጠቀሙን ያስታውሳል። እንሆኝ የቤተክርስቲያናችን ውጣ ውረድ ከተጀመረ ከ ፬ ዓመት በላይ ሆኗል።
ይህ ሁሉ ውጣ ውረድ ይህ ሁሉ ክስ የመጣው ደግሞ ከሳሾች ገንዘብ ፈልገው አልነበረም።
ቢሆንማ ኖሮ ካሳ በጠየቁ ነበር።
ለስልጣን ብለውም አልነበረም።
ቢሆንማ ኖሮ ምእመን ሳይወያዩበት በቦርዱ "ጸደቀ" የተባለው መተዳደሪያ ደንብ ለተመራጭ አስተዳዳሪዎች የፈላጭ ቆራጭ ስልጣን የሚሰጥ ነበር።
ለንብረትም አልነበረም።
ቢሆንማ ኖሮ የንብረት ክስ ከተመሰረተ ፍርድ ቤቱ ያገባዋልና ይወስንላችኋል ሲባል የንብረት ክስ አንመሰርትም ባላሉ ነበር።

ነገሩ የመብት ጉዳይ ሆነና ይኸው እስካሁን እያወዛገበ ይገኛል። ለስለሰብአዊ መብት እንከራከራለን የሚሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች መብት እንንፈግ ብለው ሲዶልቱ መክረማቸውን ያያችሁት ጉዳይ ነው ። በመብቴ አልደራደርም ያለው አባል ከአባልነት እራሱን እያሸሸ ለመምጣቱ ደግሞ ምስክር መጥራት የሚያስፈልግ አልመሰለንም። ምስክሩ እናንተ ናችሁና።

፴ ብር ለይሁዳም አልበጀምና ተው ሲባል ሰሚ አልነበረም። ይህ ግን ቤተክርስቲያኑን አደኸየ እንጂ አልጠቀመም።
አቶ ኃይሉ እጅጉ በመሰረቱት ቤተክርስቲያን አዳራሽ ለመብት ቆመሃልና አትገባም ሲባሉ የዓይን ምስክር ነበርን። ነበራችሁ።
አቶ ሙላው ወራሽ እንደ ወረደባቸው አሉባልታና የስም ማጥፋት ዘመቻ አገር ለቀው ይወጣሉ ብለው የጠበቁ ቢኖሩ የሚያስገርም አልነበረም።ያ ግን አልሆነም።

ደጋፊም ተቃዋሚም አሁንም አንድላይ ነን። አሁንም አንድ ላይ እያስቀደስን ነው ማለት እውነት ነው። ጸሎታችንን እኩል ይሰማል ማለት ግን አጠያያቂ ይሆናል። ትላንት ከአዳራሽ ያስወጡ የነበሩ እራሳቸው እንደወጡ ያያችሁት ነውና መድገም አያስፈልግም።

ሰባት ጊዜ ሽማግሌ አናግረናል የሚሉት የመብት ተከራካሪዎች፡ ሰባቱንም ጊዜ ከሽማግሌዎች ጋር በአክብሮት ተወያይተን ተለያይተናል ብለው በልበ ሙሉነት ይናገራሉ። በምስጋና የተለያዩት የመብት ተከራካሪዎች፣ የሚኮሩበት ጉዳይ ቢኖር ሽማግሌዎቹን ማሳመን መቻላቸው ብቻ ሳይሆን ከመሃከላቸው ደጋፊና አብሯቸው የሚታገል ማትረፋቸው ነው። የዛሬ ሳምንት በቤተክርስቲያን የቦርድ መሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ሁለቱም ወገኖች ታረቁ ተብሎ ሲነገር ሕዝቡ እልል ሲል ያየ ቢያለቅስ ምን ይፈረድበታል? ሁኔታው ግን ሰዓታትም ሳይቆይ እርቅ ፈርሷል ተባለና ተቀየረ። ማን እንዳፈረሰው ደግሞ ሽማግሌዎቹን መጠየቅ ይሻላል እንላለን።

የመብት ታጋዮቹን ደገፋችሁ በሚል የወሲብ አሉባልታ የተነዛባቸው ጠነከሩ እንጂ ሸብረክ ሲሉ አላየንም። ባልሰሩት የነፍስ ግዳይ የተወነጀሉት አሁንም እስር ቤት ገብተው አላየንም። ከመብት ተከራካሪዎቹ ቃለ አባባል እንውሰድ " እኛ የእምነትና የእውነት ድሃ አይደለንም" የሚል ነው። ፍርድ ቤት ይለየን እንደተባለው እነሆ ፍርድ ቤት እየለየው ነው። ማሸነፍን ግን አላየንም።

ውድ አንባብያን ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት የቦርድ አባላት ከሳሾችን ከዓመት በፊት ከቤተክርስቲያን እናባራችሁ ብለው በወሰኑባቸው ማግስት አታባርሩንም በሚል ስማቸው ተካቶ ከነበረው 28 ተባራሪዎች ውስጥ የሆኑ ምእመናን ክስ መመስረታቸው ይታወሳል። በመሆኑም የነበረውን በየጊዜው የፍርድ ቤት ውሎ መረዋ በወቅቱ የዘገበው ጉዳይ ነበርና ዛሬ ወደ ኋላ ተመልሶ ሁኔታውን በመተንተን ጊዜአችሁን ከመሻማት ይቆጠባል። ነገር ግን የዛሬ ዓመት ክሱን እናቁም በማለት ከሳሾች ከደጋፊዎቻቻው ጋር በመስማማት ክሱን ቢያቆሙም ቦርዱ እስከዛሬዋ የፍርድ ሰዓት ድረስ ለጠበቃ ያወጣንውን 89,000 ብር ይክፈሉን ሳይከፍሉን ክስ አናነሳም ብለው ሲከራረሩ ቆይ ተው ነበር። በዚህም መሰረት በዛሬው እለት ዳኛው የዚህን ክርክር የመጨረሻ ውሳኔ በመስጠት ገንዘብ መጠየቅ አትችሉም ብለው ብይናቸውን ሰጥተዋል። ይልቅስ ይላሉ ዳኛው ይህንን የእምነት ጉዳይ በቤተክርስቲያን ደንብ በውስጥ ለመፍታት ብትሞክሩ መልካም ነው። በማለት ምክራዊ ብይንም ሰጥተዋል። ከሳሾች ለቦርድ አባላት ፩ ብር (አንድ ብር) እንዲከፍሉ እንደተወሰነባቸው ደግሞ የነገሩን የመብት ተከራካሪው ቡድን አባል ለዚህ ምእመናንን እርዳታ አንጠይቅም በማለት እየሳቁ ነበር።

ይህ ቦርዶቹ የሚጠይቁት የጠበቃ ገንዘብ ባለፈው አወጣን የሚሉትን ከ140,00 ብር በላይ የሆነውን አያጠቃልልም። በቅርቡ መረዋ የደረሰውን የቦርድ አባላት ባለፈው ፩ ዓመት ተኩል ለጠበቃ ከፈልን ብለው ፍርድ ቤት ያቀረቡትን የ 89,000 የወጭ ሰንጠረዥና ከሳሾች በሁለት ዓመት ለጠበቃ ከፈልን የሚሉትን 21,593 ብር የወጭ ሰንጠረዥ ያጠቃለለ በገጹ ላይ እንደሚያትም ቃል ይገባል። ከየትም ይሁን ከየት ማንም ከፈለው ማ ከፋዩ የቤተክርስቲያናችን አባላት ያዋጡት ገንዘብ ነውና። ለአባላት ይጠቅም ዘንድ በእጃችን ያለውን ማናቸውንም መረጃ እንዳስፈላጊነቱ ለማሳወቅም እንደምንጥር ሰንናገር በእርግጠኝነት ነው።

ለመንፈሳዊ አባቶች ያለንን አድናቆትና አክብሮት እየገለጽን የኛን ወገን ዜና ማሰራጫ ሌላ መድረክ ስለሌለን ይህንን የመተንፈሻ ገጽ መጠቀማችንን እንዲረዱልን እንወዳለን።

ውድ ምእመናን ከኛ ወገን የሚተላለፍ መልእክት አለን

ከጎናችን ሆናችሁ ለከረማችሁ፣ ለእውነት ስለቆማችሁ፣ ለተሰደባችሁ፣ ለተባረራችሁ፣ ሁሉ ሚካኤል ዋጋችሁን ይክፈላችሁ እንላለን። እኛና እናንተ እንቅልፍ ተኝተን እናድራለን እንቅልፍ ያጡ ሌሎች ናቸው።
እኛና እናንተ በእሳት ተፈትነን የሕይወት ጓደኛ ሆነናል።
በየወንዙ የሚማማሉት ሌሎች ናቸው።
እኛ ትናንትናም ዛሬም ትክክል ነበርን፣ ለሰላምና ለአንድነት ታግለናል።
አቋማቸውን እንደጥላ የማያምኑት ሌሎች ናቸው።

ሚካኤል ፍርድ እየሰጠ ነው። ለክፋት በቆመው ላይ የዘላለም ፍርድ ይስጥ።

እኛ ማንንም አንጠላም ለሚጠሉን እንጸልያለን።
በማንም ላይ አንፈርድም፣ በሚፈርዱ እናዝናለን።
ማንም ከስራ እንዲወጣ አንፈልግም፣ ይህን ለሚያስቡ ሱባኤ እንገባለን።
በማስፈራራት አንፈራም ከጥል ይልቅ ለፍቅር እንሰግዳለን።
ቤተክርስቲያናችን እንደሚኖር እኛ ግን እንደምናልፍ እናምናለን።
ቤተክርስቲያን የአባቶችና የክርስቲያን ስብስብ እንጂ ሕንጻና ገንዘቡ ነው ብለን ለደቂቃም አናምንም።

ለሰላም እንጸልይ።

እንኳን ደስ አለን።

Monday, January 23, 2012

የጊብሰን የጠበቆች ስብስብ የሕግ ጠበቃ / THE GIBSON LAW GROUP ATTORNEYS AT LAW

 
THE GIBSON LAW GROUP
ATTORNEYS AT LAW 1801 N. HAMPTON RD., STE. 370
DESOTO,TEXAS75115
my.lawyer@sbcglobal.net
Telephone (972) 291-9300 Facsimile (972) 291-0636
January 10, 2012
Via Facsimile (214) 224-7555 Via Facsimile (214) 296-9662
 
Steven C. Metzger
3626 N. Hall St., Ste. 800
Dallas, TX 75243
 
Bruce Thomas
1825 Market Center Blvd., Ste. 200
Dallas, TX 75207
 
Re: Mekonen, et al. v. Retta, et al.
Cause No. 10-05578-E in the 101st District Court
Gentlemen:
This letter is sent pursuant to Texas Rule of Evidence 408 and is intended for settlement purposes only.
I have been informed that your clients defendants Dr. Girma Wolde Rufael and Abera Pitta were recently defeated for re-election to the St. Michael's board of trustees. I have also been informed that the current board desires to resolve this lawsuit amicably, to move past our clients' dispute, and to return St. Michael's to the peaceful sanctuary it once was.
To that end, my clients and the 150 or so current and former members of St. Michael's who support them spiritually and financially are prepared to forgo any further challenges, provided your clients lay down their swords as well. More specifically, the plaintiffs in this case, and all those who support them, are prepared to forego planned federal litigation provided that your clients dismiss their claims, suspend all of the recent amendments to the bylaws, reinstate all disenfranchised members, and appoint a committee representing all of the interests of the church to review and, if necessary, revise the existing bylaws.
I recognize that this is not in the nature of a traditional settlement proposal and may be difficult to document, but you know_ that this is not a traditional case. I also suspect that, regardless of your clients' formal position in this lawsuit, both you as experience counselors and they recognize that this dispute will continue in one fashion or another in one venue or another until the parties truly achieve peace. Please, therefore, understand and encourage your clients to accept that it is peace my clients desire. As such, we trust that this proposal will be received with the same good faith that it is made.
 
Counsel
1110/2012
Page2
Finally, I understand that the board of trustees has a meeting this evening. I would ask that you present this proposal to them immediately, so that they will have adequate time to consider it this evening.

Thank you.
David . Gibson cc: Clients

Wednesday, January 18, 2012

It is Blessing to live this day and able to communicate to you. NO NEWS IS GOOD NEWS!

      ውድ ምዕመናን! የእግዚአብሔር ሰላምታችንን እናቀርባለን።

ምንም ጊዜው ቢራዘም፣ የሰላም ኮሚቴ ሥራውን እየሠራ ነው። የሕዝብንም አደራ እንደጠበቀ ነው።  ይህ በግንቦት 2010፣ ከ200 ያላነሱ ምዕመናን የመረጠው 9 የሰላም ኮሚቴዎች  ሥራችን ወደ ማገባደድ ላይ ናቸው። ሥራቸው ተፈፀመ የሚያሰኘው ሪፖርታቸውን ለታዘዙት አደራ ከፈፀሙ በኋላ እስከሚያቀርቡና ምዕመናኑ እስከሚያሰናብታቸው ድረስ ነው። ይኸንንም ለመፈፀም የሚያስፈልገው፣ ከአንድና ከሁለት ጊዜ በማይበልጥ፣ ከኮሚቴና ከንዑስ ኮሜቴዎች ጋር ስብሰባ ካደረገ በኋላ ታላቅ የሕዝብ ጥሪ እንደሚያደርግ ለምዕመናን ለማሳሰብ እንወዳለን።  ትዕግሥት እንደማር ወለላ ትጣፍጣለች።

የሰላም ኮሚቴ 
የሕዝብ ግኑኝነት ክፍል።  

Monday, July 25, 2011

The latest Information to the public from The USt.Michael PRSCommette...



Information Extarcted from MERWA... on 7-25-2011


የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጠ

ውድ ምእመናን እንደምን ከረማችሁ እኛ በፈጣሪ ቸርነት እስካሁን አለን። ምነው ጠፋችሁ?  ብላችሁ ለጠየቃችሁን መልእክት ለጻፋችሁልን ሁሉ አለን ክብሩ ይስፋ ለመድኅኒዓለም  እንላለን። ከ ሁለት ቀን በፊት የ5ኛው districte ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በወይዘሮ  ጥሩአየርና  በአቶ ዳግም በተመሰረተው የቦርድ አባላት ያለአግባብ የስልጣን አጠቃቀም ክስ ላይ ብይን መስጠቱን ለአንባብያን መናገር እንወዳለን። መረዋ  ብይኑን ሙሉ ለሙሉ አንባብያን እንድታነቡት ሲያቀርብላችሁ እራሳችሁ አንብባችሁ ግንዛቤ  እንድትወስዱ በማሰብ ነው። በተከበሩት ዳኛ ኤልዛቤት ሜየር የተጻፈው የብያኔ  ትችት እንደሚያስረዳው፣ ይግባኝ ባዮቹ ከሳሾች የቤተክርስቲያኑ የቦርድ አባላት አላግባብ ስልጣናቸውን ተጠቅመው መተዳዳሪያ  ደንቡን መቀየራቸው አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው መክሰሳቸውን ተነተርሶ የቀረበ  ክስ መሆኑን አስታውሶ ክሱ በመብት መደፈር አኳያና የቤተ ክርስቲያኑ ንብረት ይገባኛል ጥያቄ አንስቶ ቢሆን ኖሮ ፍርድ ቤቱ መግባትና መወሰን ይችል እንደነበር አውስቶ ነገር ግን በመተዳደሪያ  ደንቡ ላይ ብቻ ያተኮረ ስለሆነ ይህ ደግሞ በውስጥ መፈታት ያለበት እንጂ ፍርድ ቤት በእምነት ውስጥ ጣልቃ  መግባት የለበትም የሚል ብዙ ተመሳሳይ የቆዩ ውሳኔዎችን በመጥቀስ የበታች ፍርድ ቤት ቦርዱ የመተዳደሪያ  ደንቡን መቀየር ይችላል ብሎ  የበየነውን ውሳኔ አጽንቶ ወስኗል። የቤተክርስቲያን ቦርድ አባላት ክሱ በውሸት የተመሰረተ  የቦርድ አባላትን ስራ ለማስፈታት የተመሰረተ  መሆኑን የይግባኝ ፍርድ ቤቱ እንዲወስንላቸውና  ካሳ  እንዲጥልላቸው ያቀረቡትን ሳይቀበለው ቀርቷል።

ለምን ታዲያ የንብረት ይገባኛል ጥያቄውን ከመጀመሪያው አላነሳችሁም ብለን ያነጋገርናቸው ለጉዳዩ  ቅርበት ያላቸው ግለሰቦች የነገሩን ቢኖር ከመጀመሪያው ይህ  ሃሳብ ቀርቦ የከሳሾች ፍላጎት የቤተክርስቲያኑን አባላት መብት ለማስጠበቅ እንጂ ለመበታተን ስላልነበር ሃሳቡ ተነስቶ  ውድቅ እንደተደረገ ለመገንዘብ ችለናል።

ባሁኑ ሰዓት ግን የንብረት ይገባኛል ክስ ቢመሰረት ማንም ምእመን ሊቀበለው የሚችል ለመሆኑ በሂደት በቤተክርስቲያኑ አባላት ላይ የደረሰው በደልና  አሁን ቤተክርስቲያኑ ያለበትን  በማሰብ መናገር ይቻላል ብለው እንደሚያምኑም ለመረዳት ችለናል።

መረዋ  በእትምት ጅምሩ ላይ የጠቆማቸው ሁሉ ተራ  በተራ ተፈጻሚ ሆነዋል።

ካህናት ተባረዋል
አባላት ተበትነዋል
የስደት ሲኖዶስ ከበራፍ ቆሞ እየጠበቅ ነው
እምነት ሳይሆን ስልጣን፣ አባላት ሳይሆኑ ተመራጮች ፈላጭ ቆራጭ ሆነዋል።
የነበረው ገንዘብ መንምኗል፥
ፖለቲከኞች መሰባሰቢያ  ሲያገኙ አማንያን ከስብሰባ  ታግደዋል
በእምነት ሳይሆን በፖሊስ ለማስፈራራት ተሞክሯል
የቦርድ አባላት ወንጀል በይቅርታ  ሲታለፍ ግለሰቦች ወደፍርድ ቤት በመሄዳቸው ወይም ቦርዱ የሚደረገውን በመቃወማቸው ነፍሰገዳይ ዝሙተኛ ሌባ ሴሰኛ እየተባሉ ከእግዜር በተላከ ቁጣ የሞት ፍርድ ሳይቅር እንደተፈረደ  ሁሉ ተጽፏል።
በአባላት ላይ የክፍያ  ጫና  ተጥሏል።
በዘር እንዲከፋፈል ተደርጓል
የስደት ሲኖዶስ አባላት ሰፈር ተወለጆች እንዲጠናከሩ ሲደረግ ሌሎች በዘራቸው ተወንጅለዋል።
ሲፈርዱ የነበሩ ፈራጆች ዛሬ ተፈርዶባቸዋል።
የቤተክርስቲያን መስራቾች በመመስረታቸው ተነቅፈዋል ወዘተ

ልንል የፈለግነው ያላሰብነው አዲስ ክስተት አልተፈጠረም ለማለት ነው
ባጋጣሚ ትላንትና የደረሰን ዜና  ደግሞ  ወጣት የቤተክርስቲያን ልጆች ጥያቄ  አቀረባችሁ ተብለው መባረራቸውን መስማታችን ነው። ጥያቄው ምን ነበር ስንል
ለምን የረባ  ምሳ አትሰጡንም?
ገንዘብ የለንም ካላችሁ ለምን መብራትና ቴሌቪዥን ግዢ ሄዳችሁ?
በእኛ ስም ከበጎ አድራጊዎች የተገኘ ገንዘብ የት ገባ?
ሳንማር የምንመረቀው እንዴት ነው? የሚሉ እንደ ነበሩ ለመረዳት ችለናል።

እነዚህ  እዚህ የተወለዱና  ያደጉ ሕጻናት ደግሞ ፖለቲካውም አይገባቸው ውሸትም አይዋጥላቸው፥

መረዋ ላለፉት 5 ዓመት ከልባቸው ለእውነት ለፍትህ ለመብት ለታገሉ ምእመናን በሙሉ ያለውን አክብሮትና አድናቆት እየገለጸ ወደፊትም በዚህ መልክ ለሚነሱና ካሁን በኋላ  የንብረት ጥያቄ  ለሚያነሱ  ሁሉ ድጋፉን ለመለገስ ወደ ኋላ  እንደማይል ካሁኑ ቃል ይገባል።

የማንም መብት ሲጣሰ የግል መብት እንደተጣሰ  መቁጠር ትክክለኛ  ውሳኔ  ነው።

የሚሸነፍ ሰው ለመብቱ የማይነሳ ብቻ  ነው።

ሰላምና ፍቅር ለሁላችሁ ይሁን፥
http://www.5thcoa.courts.state.tx.us/cgi-bin/as_web.exe?c05topin.ask+D+510527
የፍርድ ቤቱን ውሳኔ እንዳለ  ለማንበብ  

Thursday, March 24, 2011

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ PR witnessed at court hearing

Compiled and posted for your edification FROM a true resource MEREWA
   የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ  
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE   Public Relations Office Staff has witnessed on this day 3-23-2011 the Court Hearing.
 
After asking, pleading and begging for a meeting with the St. Michael Church Board and Board Members for over two years (22 June 2008 to 15 January 2011)  we as a committee have agreed to attend the legal venue. We have come to conclusion that this is the only way the board members can understand.  This committee stands for the majority public. Elected by the public. We will update the public as information is avialable. We will announce when we are completing our job. Please, read the following exerpts from መረዋ MEREWA:

የዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ

 
እንደምን ከረማችሁ ምእመናን

የተለየ ነገር ሳይኖር በተደጋጋሚ እናደርገው እንደ ነበረው በተከታታይ ባለመውጣታችን ምን ነካችሁ?  ላላችሁን። መረዋን አትግደሉብን ብላችሁ ለጠየቃችሁን። መረዋ ላይ ካልወጣ እውነት አይደለም ላላችሁና እምነት ለጣላችሁብን ሁሉ ምስጋናችን ወሰን የለውም። ዋሽተን ከምንከበር ይልቅ እውነቱን ተናግረን ብንወገር እንደምንመርጥ መናገር ደግሞ እውነትነቱ አንደማያጠራጥር ምስክሮቻችን እናንተ  ናችሁ።  በመሆኑም እንደ ተለመደው የዛሬን  የፍርድ ቤት   ውሎ እናካፍላችሁ
 
ባለፈው እትምታችን እንደ ነገርናችሁ  የዛሬው ቀጠሮ በ 192 የካውንቲ ችሎት በዳኛ ስሚዝ ፊት የተደረገ ክርከር ነበር። ባለፈው እረዳት ዳኛ የቦርዱ ሹማምንት ከከሳሾች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን የመመለስ ብሎም የቤተክርስቲያኑን ዶሴዎች የማሳየት ግዴታ አለባችሁ ብለው የወሰኑትን ውሳኔ በመቃወም የቦርዶቹ ጠበቃ  ለዋናው ዳኛ ስሚዝ ይግባኝ ማለታቸው ይታወሳል። የዛሬው ቀጠሮ ከመድረሱ በፊት ባለፈው በቦርዱ ላይ ተጥሎ የነበረውን እገዳ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እንዳነሳላቸው የዘገብነው ጉዳይ ነው።

በዛሬው  እለት የተከሳሾች ጠበቃ ለፍርድ ቤቱ በ march 21st ያስገቡት  ማመልከቻ ለከሳሾች ጠበቃ እንዳልደረሳቸው ለፍርድ  ቤቱ ሲናገሩ ፍርድ ቤቱ ለምን? ብሎ  የተከሳሾችን ጠበቃ  ሲጠይቅ መልሳቸው በfax ልከናል የሚል  ነበር። ፋክስም እንዳልደረሳቸው የተናገሩት የከሳሾች ጠበቃ ባላዩት ማመልከቻ  ላይ ምንም ውሳኔ  ሊሰጥ  እንደማይቻል ተናግረው ዳኛው ተስማምተዋል። ዳኛው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በሃይማኖት ጣልቃ  አትግቡ ብሏልና ለምን ጉዳዩን አየዋለሁ? ብለው ለጠየቁት ጥያቄ የተከሳሾች ጠበቃ  እኛም የምንለው እሱን ነው ብለው ሲመልሱ፣ የከሳሾች ጠበቅ ግን የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የወሰነው በእገዳው ላይ እንጂ በክሱ ይዘት ላይ አይደለም በማለት ተከረክረው ለዚህም በውሳኔው መደምደሚያ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን 
ፍሬ ሃሳብ ሳይተችበት ለዳኛ ስሚዝ ማስተላለፉን ጠቅሰዋል። የከሳሾች ጠበቃ  አያይዘውም አሁንም ቢሆን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ አልስማማም ያ  እንዳለ  ሆኖ ለክቡር ፍርድ ቤቱ ልጠይቅ የምፈልገው እነዚህ የቦርድ አባላት እንደ ፈለጉ ሕግ መቀየር ከቻሉ ነገ  አዲስ ሕግ አውጥተው ንብረቱን ወስደው ቤተክርስቲያኑን ሸጠው ወደ ጃማይካ  ቢሄዱ ምን የሚያግዳቸው ነገር አለ። እዚህ ቤተክርስቲያን አባል መሆን ለምን ያስፈልጋል?  ፈላጭ ቆራጩ ቦርድ እንጂ አባላት ምንም መብት የላቸውም። የከሰሰ  ከአባልነት ይባረራል ካሉ። አባል ለመሆን ማመልከቻ  አስገብቶ  የቦርዱን ፈቃድ መጠየቅ ካለበት ስልጣኑ የምእመናን ሳይሆን የቦርዱ ነው ብለዋል። ስለሆነም ቦርዱ ነገ  ሕጉን  ቀይሮ ምንም ማድረግ ይችላል አባል ምንም መብት የለውም ብለው ለፍርድ ቤቱ አሳስበዋል። በተጨማሪም ይህ ቤተክርስቲያን የ  501 C ፈቃድ ያለው እስከ ሆነ ድረስ  የፌድራልና የስቴት ሕግ የመከተል ግዴታ  አለበት በሃይማኖት ሽፋን ወንጀል መስራት አይችሉም ብለዋል። የተከሰሱት የቦርድ አባላት የራሳቸውን ሕግ እንኳን የማያከብሩ ናቸው ለዚህም የምርጫቸውን ሁኔታ መመልከት ይቻላል በማለት ተከራክረዋል። የተከሳሾች ጠበቃ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ከወሰነው ውጭ ፍርድ ቤቱ ምንም ማድረግ አይችልም ብለው ዛሬውኑ ክሱ ተሰርዞልን እንሰናበት ብለው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ነበር።

በመጨረሻም ዳኛው ሁለቱ ጠበቆች ተስማምተው የመከራከሪያና  የፍርድ ሃሳባቸውን ከዚህ በፊት ከነበሩ ተመሳሳይ  የተለያዩ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ጋር እንዲያቀርቡላቸው ሁለት ሳምንት ሲሰጡ ስምምነቱን አስመልክቶ የተከሳሽ ጠበቃ ጽፈውና ፈርመው ለከሳች ጠበቃ እንዲያሳልፉ የከሳሽ ጠበቃ ደግሞ ፈርመው ለፍርድ ቤቱ እንዲያቀረቡ ነግረዋቸዋል።

ዳኛው የሁለቱን መከራከሪያ ነጥብና የፍርድ ሃሳብ ካዩ በኋላ ማስረጃ መስማት እንደሚያስፈልግም ሆነ ክርክሩን ለመክፈት ወይንም ለመዝጋት ውሳኔ  ለመስጠት ለ APRIL 15 ቀጠሮ  ሰጥተው የእለቱ ችሎት  ተፈጽሟል።

በተጨማሪም በወይዘሮ ጥሩአየር እና  በአቶ  ዳግም ከሳሽነት ተመስርቶ በዳኛ  እስሚዝ የቦርዱ አባላት ካለ አባላት ፈቃድ ሕጉን መቀየር ይችላሉ ብለው የበየኑት ብያኔ  የሚታወስ ነው። ውሳኔውን በመቃወም ከሳሾቹ ለይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ይግባኝ  ማለታቸው ይታወሳል። ስለሆነም ጉዳዩን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እያለ ከሳሾች ፍርድ ቤቱ ያለውን መረጃ ተመልክቶ  ውሳኔ  ይስጠን ቢሉም የቦርዱ ጠበቆች የለም የቃል ክርክር እንፈልጋለን በማለታቸው የቃል ክርክሩን ለማዳመጥ ጉዳዩ ለመጭው MAY 4,  2011, 1:00 P.M., 5th District Court of Appeal of Texas, 600 Commerce, George L. Allan Bldg. Suite #200   መቀጠሩን ልንነግራችሁ እንወዳለን። 
ማንኛውም የቤተክርስቲያን ምእመን  በፍርድ ቤት በመገኘት ክርክሩን ማዳመጥ  እንደሚችል ስንነግራችሁ በደሰታ  ነው።
የቦርድ አባላት የማያልቅ ገንዘብ ስላላቸው ብዙ የማቆያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀሙ ትላንት ፍርድ ቤት የተነገረ ሲሆን፣ መብታቸው የተደፈረው ምእመናን ደግሞ  ፈጣሪንና ደጋፊዎቻቸውን ይዘው መታገላቸውን እንደማያቆሙ ከሂደቱ መገንዘብ ይቻላል::
  መረዋ ለምእመናን የሚጠይቀው ነገር ቢኖር!  
  መብት የሌለው አባልነት ምንድነው?       የሚል ይሆናል።
 
 መረዋም የዛሬውን ዘገባ  በዚሁ ያበቃል::
 
United St. Michael Peace Seeker Resolution Committee will follow up the truth and justice. 
 The public has imposed responsibility and we will update every move there is.  Our MOTO is: Honest, faith, peace, justice, mercy, love, humble, integrity, pride.
 
Public Relation Office.

Friday, January 28, 2011

United St. Micheal Church Peace Resolution Seekers Committee 3rd General Meeting 1--23-2011, Report from PR

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ                 UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE 
       Meleket4u@gmail.com

1-23-2011
                                          ጠቅላላ የምዕመናን ስብሰባ

የዛሬውን አጠቃላይ ስብሰባ በ15:15 ፒ ኤም ም/ሊቀመንበሩ አቶ ግርማቸው አድማሴ ስብሰባውን በቄስስ መስፍን ደምሴ ቡራኬ በመስጠት በአንድነት በፀሎት ከፍቱልን። 5 ኤም ስብሰባው ተዘግቷል።

ከተሰጡትም ገንቢ አስተያየቶችና መልዕክቶች መካከል፤
ሀ. የኮሚቴው ዋና ሥራ የሆነው የሕግ አገልግሎት ጉዳይን በተመለከት መሰረታዊ ጥያቄዎችና ዓላማዎች ግልፅና አጭር በሆነ መልክ ለምዕመናን መግለጫ እንዲሰጥ።
ለ. የመልአከ ሣህልን በሥራ ጉዳይ ምክንያት ወደ ሌላ ግዛት መሄዳቸውን አስመልክቶ በ 1-28-2011 በሚደረገው የሽኝት ዝግጅት ላይ ከዓርብ ጉባኤ ጋር በመቀናጀት አሰኛኘት እንዲደረግላቸው።
ሐ. በቅርቡ በሚካሄዱት የፍርድ ቤት ቀጠሮዎች 2-7-2011፣ በ3 ፒ ኤም እና 2-10-2011፣ በ9 ኤ ኤም ላይ መገኘት የሚችሉ ምዕመናን አንዲገኙ።
መ. “ቤተክርስቲያን ተከሷል” የሚባለው የተዛባ ውዥንብር የሚወገድበት ትክክለኛው የፍትሕ ጥረት ለምዕመናኑ በመግለፅ የሚረዱበት መንገድ እንዲፈጠር።
ሠ. በዓርብ ጉባኤ እየተዘጋጀ ባለው ሦስተኛ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ኮሚቴው ትብብሩን እንዲያደርግና መድረኩንም በመጠቀም ለሕዝቡ መልእክት እንዲያዘጋጅ።
ረ. የሕግ ጉዳዩን በተመለከተ ለሚያስፈልጉት የኃሳብና የገንዘብ ዕርዳታ ቅንጅትና ትብብር በመላ ምዕመናኑ የሚካሄድበትን።

ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

Wednesday, January 12, 2011

Message from URC Public Relations Office "MELEKET4U"

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ  
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
                     “መለከት”       
     meleket4u.blogspot.com
“ጠቅላላ የምዕመናን ስብሰባ ጥሪ”
(የሕዝብ አደራ መጠበቅ ስለ አለብን፣ በተፈጠረው ወቅታዊ አጋጣሚ ችግሮችና ሐዘኖች ምክንያት የተሰረዘው የምዕመናን ስብሰባ ጥሪ እንደገና ይቀጥላል። ብርታቱን ለሁላችንም እግዚአብሔር ይስጠን።)
ቀኑ፡-ጥር 15 ቀን 2003 እሁድ
January 23, 2011, Sunday
ሰዓት፡-1፡00 ፒ ኤም፡ምሳ አለ።
ቦታው፡- Dream Club, 7035 Greenville Ave #E, Dallas, TX 75231-5109 (214) 368-4981 ወይንም (469) 879-8650

Saturday, December 18, 2010

United St. Micheal Church Peace Resolution Seekers Committee Postpond the 3rd General Meeting that will be held on 12-19-10

United St. Micheal Church Peace Resolution Seekers Committee Postpond the 3rd General Meeting that will be held on 12-19-10, 1:00 p.m. at Dreams Club for mid-January 2011.

       የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
12-16-2010
                “መለከት የጠራው”     “ጠቅላላ የምዕመናን የስብሰባ ጥሪ ቀን መተላለፍ”http://www.meleket4u.blogspot.com/                                           meleket4u@gmail.com
በኮሚኒቴአችን አባላት በደረሰው ድንገተኛ ሐዘን ምክንያት፣ የስብሰባውን ቀን እስከ ጃኑዋሪ 2011 አጋማሽ ድረስ ያስተላለፍነው መሆናችንን እናስታውቃችኋለን።
በደረሰባቸውም ድንገተኛ አደጋም የኃዘናቸው ተካፋይ መሆናችንንም ከልብ እንገልፃለን።


 ኮሚቴው።

የስብሰባ ቀን ጥሪ መተላለፍ

የተባበሩት የቅዱስ  ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ 
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS  COMMITTEE 
http://www.meleket4u.blogspot.com/                                                MELEKET4U@GMAIL.COM

በመሃከላችን በተከሰተው ያልተጠበቀ ድንገተኛ ሐዘን ምክንያት በነገው እለት እሑድ ከቅዳሴ  በኋላ  በ 1:00 PM  ተጠርቶ  የነበረው የምእመናን ስብሰባ ወደ እሚመጣው ወር አጋማሽ እንዲተላለፍ የተወሰነ መሆኑን ለአባላትና  ለደጋፊዎቻችን እናስታውቃለን። ስብሰባው መቼና የት እንደሚሆን ወደፊት እንነግራችኋለን።

በዚህ አጋጣሚ የዚህ ኮሚቴ  አባላት በደረሰው ሐዘን ከልብ መነካታችንን እየገለጽን ወጣቱን ከመላእክት ዘማርያን እንዲቀላቅለው ቤተሰቦቹን ደግሞ ብርታትና  መጽናናቱን እንዲሰጣቸው እንለምናለን።

ኮሚቴው




Thursday, December 9, 2010

Reporting to St. Michael's MeMenan the result of Elders meeting with UR Commette

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
ይህ ሪፖርት ከኮሚቴው የተላፈ ነው።
12-04-10
የቅዱስ ሚካኤል አስተዳደር ቦርድ ሰላምና ለሽምግልና እምቢተኝነቱን በድጋሚ አረጋገጠ።
የተከበራችሁ ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተሰቦች አንደምን ሰነበታችሁ።
ባሇፈው በ9/23/10 ከቤተክርስቲአናችን ሰላም ወዳድና ያለትን ችግሮች ሁለ በሰላም መንገድ መፍታት ይቻላል በሚለ ኃይሎችና በእኛም ኮሚቴ ድጋፍ አግኝቶ በአቶ ሰይፉ ይገዙ ሰብሳቢነት የሚመራ የሽምግልና ኮሚቴ ሥራውን መጀመሩን መግለጻችን የሚታወስ ነው። ይህ የሽምግልና ኮሚቴ የቦርዱ የሚለ ጥቂት የሰላም መንገድ ምን እንደሆነ ያልገባቸው ግለሰቦች ሲፈጥሩት የነበረውን ሁካታ እያዳመጥን ተጨባጭነት እስኪኖረው ድረስ ሪፖርት ከማቅረብ ተቆጥበን ነበር። አነሆ አሁን ደግሞ በመጨረሻ የሽማግሌዎቹ ኮሚቴ ያክናወኑትን ጉዳይ ለቅዱስ ሚካኤል የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ለማስረዳት በ12/1/10 ከምሽቱ ስድስት ሰዓት ላይ በክራውን ፕላዛ ሆቴል በተስማማንበት መሰረት ተሰባሰብን የሽማግሌዎቹም ኮሚቴ በአቶ ሰይፉ ይገዙ መሪነት አቶ ዳኜ፣ ዶክተር ታየ፣ አቶ ጌታቸው፣ አቶ ኪዳኔና አቶ በትሩ ሲሆኑ ሰብሰባውም በጸሎት ተጀመረ ሰባሳቢው አቶ ሰይፉ አጠቃላይ ሁኔታውን አቅርበው ሲጨርሱ ሌሎቹም ሽማግሌዎች በየተራ የየራሳቸውን አስተያየት አስደምጠውናል::
ውድ የሚካኤል ቤተሰቦች ሆይ! የተከበሩት ሽማግሌዎች ያዓቅማቸውን ያህል መጣራቸው ግልጽ መሆኑን ብንገነዘብም በሁለም መንገድ ሰላምን የሚሸሸው (የማይፈልገው) ቦርድ የቤተክርሰቲአኑን አዛውንቶች ወደ ሁሇት ወር ካደከማቸው በኋላ የምቢተኝነቱን መልስ ሰጥቶአቸዋል። በተጨማሪም የቦርዱ አባላት በቤተክርስቲአናችን ውስጥ ምንም ችግር እንደሌሇ ችግርም አሇ ከተባሇም አሁን በብዙ ስራ ስሇተጠመድን በሚቀጥሇው ዓመት ጉዳዩን እናየዋሇን እንዳለዋቸው ሲነግሩን በጣም አዘንን እናም በሽታውን የማያውቅ በሽተኛ ጉዳት እንጂ ጥቅም እንደሌሇው ቢአውቅ ብልህነት ነበር እንላሇን!
ውድ የሚካኤል ቤተሰቦች ኮሚቴአችንም አዛውንቱን ለሞከሩት ሙከራ ከልብ አመስግኖ እንዲሁም እምቢተኛው ቦርድ ለሰጣቸው መልስ ምስክሮቻችን እንደሆኑ ከአስረዳን በኋላ ስብሳባው በጨዋነት በጸሎት ተፈጽሞአል።
ለሰላምና ለፍትሕ የሚደረገው ጥረት ይቀጥላል። ይዘገያል እንጂ ፍትሕ መገኘቱ፤ እውነቱ መውጣቱ አይቀርም።
ኮሚቴው
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

Saturday, December 4, 2010

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
“መለከት” “ጠቅላላ የምዕመናን ስብሰባ ጥሪ”
http://www.meleket4u.blogspot.com/ meleket4u@gmail.com
ታኅሣሥ 10, ቀን 2003
December 19, 2010, 1:00p.m.
ምሳ! የጾም ምግብ አለ! ቦታው፡- Dreams Club, 7035 Greenville Ave # E, Dallas, TX 75231-5109 (214) 368-4981 ወይንም (469) 879-8650

Sunday, November 14, 2010

Message from URC Public Relations Office

 የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ  
           UNITED ST. MICHAEL CHURCH RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE                   
                  
ካለፈው የቀጠለ።

የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍል በሂደት ለሕዝብ/ለአንባቢያን የሚያቀርበው ያለ ጊዜ ገደብ ስለሆነ የሂደቶቹን እንቅስቃሴ በአግባቡና በወቅቱ እናቀርባለን። የሃሳብ ወይንም ኮሜንት መስጫ ቦታ ስላለን ተጠቀሙበት።

የተከበራችሁ ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተሰቦች አንደምን ሰነበታችሁ።
አንደምታስታውሱት ባለፈው በ9/23/10 ከቤተክርስቲአናችን አባላት መካከል በአቶ ሰይፉ ይገዙ የሚመራ የሽምግልና ኮሚቴ ጋር ኮሚቴአችን ተሰብስቦ አንደነበር በዚሁ ጦማር ላይ አስነብበናችሁ ነበር። አነሆ አሁን ደግሞ ባለፉት ሁለት ወራት የሽምግልናው ኮሚቴ አባላት የተወስኑ የሚካኤል አባላትና የሚካኤል የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት በየመስመራቸው ሽምግልናው ይሳካ ዘንድ ውይይቱን ቀጥለዋል ምንም አንኩዋን የቤተክርስቲያኑ ቦርድ አንካሳ ምክንያት አየደረደረ ቢገኝም ውይይቱ አንደቀጠለ ነው። በቅርቡም በሽምግልናው በኩል ያለው ሁኔታ በአጠቃላይ አናቅርብላችኋለን አስክውዚያው ቸር ይግጠመን።

ከሕዝብ ግንኙነት ክፍል
           

Saturday, September 25, 2010

ሳምንቱን ካጋጠመን

የተከበራችሁ፡ ውድ፡ ምዕመናን፡

     እንደሚታወቀው፡ የቅዱስ፡ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን፡ ችግር፡ መፍትሄ፡ ለማፈላልግ፡ እንድንጥር፡ ከመረጣችሁን፡ ጊዜ፡ አንስቶ፡ የጣላችሁብንን፡ አደራ፡ ለመወጣት በጥንቃቄ፣ በቆራጥነትና፣ በቅንነት፡እየሰራን፡ እንደሆነ፡ ልናረጋግጥላችሁ፡  እንወዳለን።  ችግሩን፡ ለአንዴም፡ ለሁሌም ለመፍታት፡ የምንችለውን፡ ሁሉ፡ በሁሉም፡ አቅጣጫ፡  እየጣርን ነው፡፡ ታዲያ፡ ሰሞኑንም፡ ከቤተክርሰቲያናችን፡ አባላት፡ መካከል፡ የተወሰኑ፡ግለሰቦች፡ ሰላም፡ መስፈን፡ ይኖርበታል፡ ከሚል፡  መርህ፡ በመነሳት፡ አዛውንቶችን፡ አነጋግረው፡ እንደነበረና፡ ሽማግሌዎቹም እንዚህን ቡድኖች ባነጋገሩ ማግስት የኛን ኮሚቴ ለማነጋገር ወስነው መበተናቸውን ለማወቅ ችለን ነበር። ግለሰቦቹን ያነጋገረው፡የሽማግሌዎቹ፡ ኮሚቴ አባላት፡ መካከልም፡ ከፊሎቹ፡ ለቤተክርስቲአናችን፡ ብዙ፡ ግልጋሎት፡ ያበረከቱ፡ በመስራችነታቸው፡ የሚታወቁ ባካባቢያችን፡ የቆዩ፡ የችግሩንም፡ አነሳስ፡ በሚገባ፡ ሲጀመር፡ ጀምሮ፡ የተመለከቱ፡ አንዳሉበትም፡ ለመረዳት ችለናል። ሽማግሌዎቹ፡ እነዚህን ሰላም እንፈልጋለን የሚሉትን ቡድኖች ባነጋገሩ ማግስት፡ሁለት፡ ቀን፡ባልበለጠ፡ ጊዜ፡ውስጥ፡ ተሰብሰበን፡ ከነርሱ፡ ጋር፡ መወያየት፡ እንድንችል፡ በሊቀመ ንበርችን፡ በኩል፡ ጥያቄ፡  አቀረቡ፡፡ አኛም፡ ጊዜ፡ ሳናባክን፡ ተሰብስበን፡ ከሁለት፡ ሰዓት፡ በላይ፡ ጉዳዩን፡ ከሁሉም፡ አቅጣጫ፡ መርምረን፡ ከጉዳቱ፡ ይልቅ፡ ጥቅሙ፡ እንደሚያመዝን፡ በመገንዘብ፡ በአንድ፡ ድምጽ፤ ተቀብለን፡ ሽማግሌዎቹን፡ ሐሙስ፡ በ6፡00PM (9/23/10) ለማነጋገር ተስማምተን በተባለው ሰዓትና ወቅት ሽማግሌዎቹን አነጋግረናል።

 ውይይቱ፡ በአካል፡ በቅዱስ፡ ሚካኤል፡ የስብሰባ፡ አዳራሽ፡ ውስጥ፡የተካያደ ሲሆን መልካም፡ ጅማሮ፡ የታየበት፡ የሁለት፡ ሰዓት ስብሰባ ነበር። ቀጣዩም፡ ስብሰባ፡ የመልክተኞቹ፡ ኮሚቴ፡ ከቤተክርስትያኑ፡ የቦርድ፡ አባላት፡ የይሁንታ፡ ደበዳቤ፡ ከዚያም፡ ለመላው፡ የቅዱስ፡ ሚካኤል፡ ምአመናን፡ በይፋ፡ ከተነገረ፡ በኋላ፡ እንደሚሆን አስታውቀናቸው፡ በቅን፡ መንፍስ፡ ተደምድሟል።

ድ፡ ምአመናን፡ ሆይ!

የቅዱስ፡ ሚካአኤል፤ ችግር፤ የመፍትሄ፤ አፈላላጊ፤ ኮሚቴ፤  የምናደርገውን፤ ጉዞ፤ ሁሉ፤ አንድ፤ በአንድ፤ በጥንቃቄ፤ አንደምናሳውቃችሁ ቃል በገባንው መሰረት ይህንንም ከሌሎች ከመስማታችሁ በፊት ከኮሚቴው እንድትሰሙት በማለት አውጥተነዋል። ወደፊትም አቅማችን፡ በፈቀደው፤ ፍጥነት፤ ሁሉንም ሂደት እንድታውቁት፡ እንደምናደርግ ቃል እንገባላችኋለን።

የሕዝብ፡ ግንኙነት፡ ኮሚቴ፡

የልኡል፡ አግዚአብሔር፡ እረድኤት፡  ይታከልበት!!

Saturday, September 18, 2010

የሰላም ጥረቱ እንደቀጠለ ነው።

ከስብስቡ ሊቀመንበር የተላከ  መልእክት

የሰላም፤ የአንድነት፣ የፍቅር  ጥረቱ አሁንም እንደቀጠለ  ነው። የምንመኘውን የምንፈልገውን ዘላቂውን ሰላም፤ አንድነት፣ ፍቅር በቤተክርስቲያናችን  ብሎም በሕብረተሰባችን ልናመጣ የምንችለው የተለየዩ  የመፍትሄ  ሃሳቦችን የያዙትን፡ በዳይ ነው የተባለውንም ሆነ ተበድሏል የተባለውን አቀራርበን ውይይት ማድረግ ሲቻልና ብዙሃኑ የተቀበለውን ማስፈጸም ስንችል ብቻ ነው። በሌላ አነጋገር ለችግራችን ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት ሁላችንም የሚያስማማንን መንገድ የመፈለግ ግዴታ አለብን። ይህ ደግሞ ብስለትን፤ ቅንነትን፤ ሐቀኝነትን፣ መተማመንን ይጠይቃል። ፈረንጆቹ እንደሚሉት(MY WAY OR  THE HIGH WAY ) ወይም እኔ  ያልኩት ካልሆነ እሞታለሁ የሚል አመለካከት ካለ ግን የተነሳንበትን የመወያየቱን መርህ ይገድለዋል።

ይህንን ካልን ዘንዳ!!በዚህም በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የተነሳው አለመግባባት ደረጃው ይለይ እንጂ ከቤተክርስቲያኑ አስተዳደር ዙሪያ "በደል ደረሰብን፣ መብታችን ተነካ፣ መተዳደሪያ ደንቡ ተሸረሸረ፣ የብዙሃን ድምፅ ታፈነ፣ ሃሳባችን አልተስተናገደም ወዘት በማለት የሚያስቡ ግለሰቦች ለችግራቸው መፍትሄ ነው ያሉትን አቅርበው መወያየት ችለዋል። በውይይቱም ተማምነው የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋም በቅተለዋል። አስተማማኝ ሁኔታም እስኪፈጸም  ድረስ  የተነሱበትን ዓላም እንደማይስቱ አሁንም ለሰላም፣ ለአንድነት፣ ለፍቅር እንደሚታገሉ፣ ሁላችንም ይህንን መርህ ከተከተልን ደግሞ ወደ  ነበርንበት መመለሱ ሕልም እንደማይሆን ያምናሉ።  

የአንድ አካባቢ ስብስብ ወይንም በብዙሃን ድምፅ የሚተዳደር አካል ለተለያዩ ሃሳቦች መፍትሄ የሚያገኘው ብዙሃኑ ተስማምቶ በተቀበለው ሃሳብ ሲመራ መሆኑን አንጠራጠርም። ይህንን አማራጭ የሌለውን አካሄድ መከተል ደግሞ ግዴታ ነው እንላለን።  እስከዛሬ በግልም ሆነ በቡድን በጽሑፍም ሆነ በቃል የተነገሩ ሃሳቦች ሁሉ  በእንዲህ ያለ አጠቃላይ ሁሉን አቀፍ ተደጋጋሚ ስብሰባ መቋጨት አለባቸው ብለን እናምናለን።  

የዚህ ጦማር  አጀማመር ደግሞ ያለምንም መደባበቅ በእውነት ላይ ያተኮረ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ያሉትን ችግሮች ሌሎች እንዲረዱት ሃሳቦችን ማንሸራሸር እንዲቻል ከሚያገኘው ጭብጥ በመነሳት አንባቢው ፍርድ መስጠት እንዲችል ለመርዳት ጭምር ነው።

የጦማሩ ባለቤቶች በ 200አባላት የተመረጠው የሰላም አፈላላጊ ኮሚቴ ሲሆን፣ ኮሚቴው እስካሁን ያከናወነውን እያደነቅሁ በዚህም መስክ ጥሩ ተግባር እንደሚያሳይ ጥርጥር የለኝም። አባላቱም የተቻላቸውን ሁሉ በማድረግ ጦማሩ የእውነት መመንጫ የመፍትሄ መፈለጊያ የእውነተኛ ዜና መቀያየሪያ መድረክ እንዲያደርገው ማሳሰቢያዬን በኮሚቴው ስም ላቀርብ እወዳለሁ። በቤተክርስቲያኑ አስተዳደር ዙሪያ የተሰበሰቡት ኃይሎችም ለሰላም፣ ለአንድነት፣ ለፍቅር ጥረቱ በጎ ምላሽ እንዲሰጡ በኮሚቴውና  በራሴ  ስም ጥሪ አቀርባለሁ።

ቸሩ እግዚአብሔር የሰላም፣ የአንድነት፣ የፍቅር አቅጣጫ ያሳየን።

የስብስቡ ሊቀመንበር

Tuesday, September 14, 2010

ሰላምን መፍጠር እንችላለን

የእግዚብሔር ጸጋና  ቸርነት በሁላችን ላይ ይደር አሜን።

እንዴት ሰነበታችሁ በክርስቶስ ወንድሞችና  እህቶች የሆናችሁ በመላ። ቶሎ እናስነብባችኋለን ብለን ስለዘገየነ ይቅርታ  እንጠይቃለን። እንዴው የሁላችሁንም ጥያቄ  ሊመልስ የሚችል የተቀነባበረ ጽሑፍ ለማውጣት በማሰብ መቆየታችንን ስንናገር ይህ እውነተኛ ምክንያት እንጂ በቂነው ተብሎ አይደለም። ተገናኝተን ለመወያየት ያለውን የጊዜ መጨናነቅ ለመረዳት ደግሞ በፈቃደኝነት የተሳተፉት ሁሉ የሚረዱት ይመስለናል። አሁን ግን ሁኔታው እየተስተካከለ  መጥቶ ከየኮሚቴው የደረሱንን መግለጫዎች ሰሞኑን እንደምናወጣ ቃል እንገባላችሁ ዘንዳ እንወዳለን።  ስለ ትእግስታችሁ ምስጋናችን በድጋሜ ይድረሳችሁ። 

ኮሚቴው

የ E MAIL አድራሻችን

MELEKET4U@GMAIL.COM