Saturday, September 25, 2010

ሳምንቱን ካጋጠመን

የተከበራችሁ፡ ውድ፡ ምዕመናን፡

     እንደሚታወቀው፡ የቅዱስ፡ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን፡ ችግር፡ መፍትሄ፡ ለማፈላልግ፡ እንድንጥር፡ ከመረጣችሁን፡ ጊዜ፡ አንስቶ፡ የጣላችሁብንን፡ አደራ፡ ለመወጣት በጥንቃቄ፣ በቆራጥነትና፣ በቅንነት፡እየሰራን፡ እንደሆነ፡ ልናረጋግጥላችሁ፡  እንወዳለን።  ችግሩን፡ ለአንዴም፡ ለሁሌም ለመፍታት፡ የምንችለውን፡ ሁሉ፡ በሁሉም፡ አቅጣጫ፡  እየጣርን ነው፡፡ ታዲያ፡ ሰሞኑንም፡ ከቤተክርሰቲያናችን፡ አባላት፡ መካከል፡ የተወሰኑ፡ግለሰቦች፡ ሰላም፡ መስፈን፡ ይኖርበታል፡ ከሚል፡  መርህ፡ በመነሳት፡ አዛውንቶችን፡ አነጋግረው፡ እንደነበረና፡ ሽማግሌዎቹም እንዚህን ቡድኖች ባነጋገሩ ማግስት የኛን ኮሚቴ ለማነጋገር ወስነው መበተናቸውን ለማወቅ ችለን ነበር። ግለሰቦቹን ያነጋገረው፡የሽማግሌዎቹ፡ ኮሚቴ አባላት፡ መካከልም፡ ከፊሎቹ፡ ለቤተክርስቲአናችን፡ ብዙ፡ ግልጋሎት፡ ያበረከቱ፡ በመስራችነታቸው፡ የሚታወቁ ባካባቢያችን፡ የቆዩ፡ የችግሩንም፡ አነሳስ፡ በሚገባ፡ ሲጀመር፡ ጀምሮ፡ የተመለከቱ፡ አንዳሉበትም፡ ለመረዳት ችለናል። ሽማግሌዎቹ፡ እነዚህን ሰላም እንፈልጋለን የሚሉትን ቡድኖች ባነጋገሩ ማግስት፡ሁለት፡ ቀን፡ባልበለጠ፡ ጊዜ፡ውስጥ፡ ተሰብሰበን፡ ከነርሱ፡ ጋር፡ መወያየት፡ እንድንችል፡ በሊቀመ ንበርችን፡ በኩል፡ ጥያቄ፡  አቀረቡ፡፡ አኛም፡ ጊዜ፡ ሳናባክን፡ ተሰብስበን፡ ከሁለት፡ ሰዓት፡ በላይ፡ ጉዳዩን፡ ከሁሉም፡ አቅጣጫ፡ መርምረን፡ ከጉዳቱ፡ ይልቅ፡ ጥቅሙ፡ እንደሚያመዝን፡ በመገንዘብ፡ በአንድ፡ ድምጽ፤ ተቀብለን፡ ሽማግሌዎቹን፡ ሐሙስ፡ በ6፡00PM (9/23/10) ለማነጋገር ተስማምተን በተባለው ሰዓትና ወቅት ሽማግሌዎቹን አነጋግረናል።

 ውይይቱ፡ በአካል፡ በቅዱስ፡ ሚካኤል፡ የስብሰባ፡ አዳራሽ፡ ውስጥ፡የተካያደ ሲሆን መልካም፡ ጅማሮ፡ የታየበት፡ የሁለት፡ ሰዓት ስብሰባ ነበር። ቀጣዩም፡ ስብሰባ፡ የመልክተኞቹ፡ ኮሚቴ፡ ከቤተክርስትያኑ፡ የቦርድ፡ አባላት፡ የይሁንታ፡ ደበዳቤ፡ ከዚያም፡ ለመላው፡ የቅዱስ፡ ሚካኤል፡ ምአመናን፡ በይፋ፡ ከተነገረ፡ በኋላ፡ እንደሚሆን አስታውቀናቸው፡ በቅን፡ መንፍስ፡ ተደምድሟል።

ድ፡ ምአመናን፡ ሆይ!

የቅዱስ፡ ሚካአኤል፤ ችግር፤ የመፍትሄ፤ አፈላላጊ፤ ኮሚቴ፤  የምናደርገውን፤ ጉዞ፤ ሁሉ፤ አንድ፤ በአንድ፤ በጥንቃቄ፤ አንደምናሳውቃችሁ ቃል በገባንው መሰረት ይህንንም ከሌሎች ከመስማታችሁ በፊት ከኮሚቴው እንድትሰሙት በማለት አውጥተነዋል። ወደፊትም አቅማችን፡ በፈቀደው፤ ፍጥነት፤ ሁሉንም ሂደት እንድታውቁት፡ እንደምናደርግ ቃል እንገባላችኋለን።

የሕዝብ፡ ግንኙነት፡ ኮሚቴ፡

የልኡል፡ አግዚአብሔር፡ እረድኤት፡  ይታከልበት!!

No comments:

Post a Comment