Saturday, December 18, 2010

United St. Micheal Church Peace Resolution Seekers Committee Postpond the 3rd General Meeting that will be held on 12-19-10

United St. Micheal Church Peace Resolution Seekers Committee Postpond the 3rd General Meeting that will be held on 12-19-10, 1:00 p.m. at Dreams Club for mid-January 2011.

       የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
12-16-2010
                “መለከት የጠራው”     “ጠቅላላ የምዕመናን የስብሰባ ጥሪ ቀን መተላለፍ”http://www.meleket4u.blogspot.com/                                           meleket4u@gmail.com
በኮሚኒቴአችን አባላት በደረሰው ድንገተኛ ሐዘን ምክንያት፣ የስብሰባውን ቀን እስከ ጃኑዋሪ 2011 አጋማሽ ድረስ ያስተላለፍነው መሆናችንን እናስታውቃችኋለን።
በደረሰባቸውም ድንገተኛ አደጋም የኃዘናቸው ተካፋይ መሆናችንንም ከልብ እንገልፃለን።


 ኮሚቴው።

የስብሰባ ቀን ጥሪ መተላለፍ

የተባበሩት የቅዱስ  ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ 
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS  COMMITTEE 
http://www.meleket4u.blogspot.com/                                                MELEKET4U@GMAIL.COM

በመሃከላችን በተከሰተው ያልተጠበቀ ድንገተኛ ሐዘን ምክንያት በነገው እለት እሑድ ከቅዳሴ  በኋላ  በ 1:00 PM  ተጠርቶ  የነበረው የምእመናን ስብሰባ ወደ እሚመጣው ወር አጋማሽ እንዲተላለፍ የተወሰነ መሆኑን ለአባላትና  ለደጋፊዎቻችን እናስታውቃለን። ስብሰባው መቼና የት እንደሚሆን ወደፊት እንነግራችኋለን።

በዚህ አጋጣሚ የዚህ ኮሚቴ  አባላት በደረሰው ሐዘን ከልብ መነካታችንን እየገለጽን ወጣቱን ከመላእክት ዘማርያን እንዲቀላቅለው ቤተሰቦቹን ደግሞ ብርታትና  መጽናናቱን እንዲሰጣቸው እንለምናለን።

ኮሚቴው




Thursday, December 9, 2010

Reporting to St. Michael's MeMenan the result of Elders meeting with UR Commette

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
ይህ ሪፖርት ከኮሚቴው የተላፈ ነው።
12-04-10
የቅዱስ ሚካኤል አስተዳደር ቦርድ ሰላምና ለሽምግልና እምቢተኝነቱን በድጋሚ አረጋገጠ።
የተከበራችሁ ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተሰቦች አንደምን ሰነበታችሁ።
ባሇፈው በ9/23/10 ከቤተክርስቲአናችን ሰላም ወዳድና ያለትን ችግሮች ሁለ በሰላም መንገድ መፍታት ይቻላል በሚለ ኃይሎችና በእኛም ኮሚቴ ድጋፍ አግኝቶ በአቶ ሰይፉ ይገዙ ሰብሳቢነት የሚመራ የሽምግልና ኮሚቴ ሥራውን መጀመሩን መግለጻችን የሚታወስ ነው። ይህ የሽምግልና ኮሚቴ የቦርዱ የሚለ ጥቂት የሰላም መንገድ ምን እንደሆነ ያልገባቸው ግለሰቦች ሲፈጥሩት የነበረውን ሁካታ እያዳመጥን ተጨባጭነት እስኪኖረው ድረስ ሪፖርት ከማቅረብ ተቆጥበን ነበር። አነሆ አሁን ደግሞ በመጨረሻ የሽማግሌዎቹ ኮሚቴ ያክናወኑትን ጉዳይ ለቅዱስ ሚካኤል የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ለማስረዳት በ12/1/10 ከምሽቱ ስድስት ሰዓት ላይ በክራውን ፕላዛ ሆቴል በተስማማንበት መሰረት ተሰባሰብን የሽማግሌዎቹም ኮሚቴ በአቶ ሰይፉ ይገዙ መሪነት አቶ ዳኜ፣ ዶክተር ታየ፣ አቶ ጌታቸው፣ አቶ ኪዳኔና አቶ በትሩ ሲሆኑ ሰብሰባውም በጸሎት ተጀመረ ሰባሳቢው አቶ ሰይፉ አጠቃላይ ሁኔታውን አቅርበው ሲጨርሱ ሌሎቹም ሽማግሌዎች በየተራ የየራሳቸውን አስተያየት አስደምጠውናል::
ውድ የሚካኤል ቤተሰቦች ሆይ! የተከበሩት ሽማግሌዎች ያዓቅማቸውን ያህል መጣራቸው ግልጽ መሆኑን ብንገነዘብም በሁለም መንገድ ሰላምን የሚሸሸው (የማይፈልገው) ቦርድ የቤተክርሰቲአኑን አዛውንቶች ወደ ሁሇት ወር ካደከማቸው በኋላ የምቢተኝነቱን መልስ ሰጥቶአቸዋል። በተጨማሪም የቦርዱ አባላት በቤተክርስቲአናችን ውስጥ ምንም ችግር እንደሌሇ ችግርም አሇ ከተባሇም አሁን በብዙ ስራ ስሇተጠመድን በሚቀጥሇው ዓመት ጉዳዩን እናየዋሇን እንዳለዋቸው ሲነግሩን በጣም አዘንን እናም በሽታውን የማያውቅ በሽተኛ ጉዳት እንጂ ጥቅም እንደሌሇው ቢአውቅ ብልህነት ነበር እንላሇን!
ውድ የሚካኤል ቤተሰቦች ኮሚቴአችንም አዛውንቱን ለሞከሩት ሙከራ ከልብ አመስግኖ እንዲሁም እምቢተኛው ቦርድ ለሰጣቸው መልስ ምስክሮቻችን እንደሆኑ ከአስረዳን በኋላ ስብሳባው በጨዋነት በጸሎት ተፈጽሞአል።
ለሰላምና ለፍትሕ የሚደረገው ጥረት ይቀጥላል። ይዘገያል እንጂ ፍትሕ መገኘቱ፤ እውነቱ መውጣቱ አይቀርም።
ኮሚቴው
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

Saturday, December 4, 2010

የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ
UNITED ST. MICHAEL CHURCH PEACE RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE
“መለከት” “ጠቅላላ የምዕመናን ስብሰባ ጥሪ”
http://www.meleket4u.blogspot.com/ meleket4u@gmail.com
ታኅሣሥ 10, ቀን 2003
December 19, 2010, 1:00p.m.
ምሳ! የጾም ምግብ አለ! ቦታው፡- Dreams Club, 7035 Greenville Ave # E, Dallas, TX 75231-5109 (214) 368-4981 ወይንም (469) 879-8650