Sunday, November 14, 2010

Message from URC Public Relations Office

 የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ  
           UNITED ST. MICHAEL CHURCH RESOLUTION SEEKERS COMMITTEE                   
                  
ካለፈው የቀጠለ።

የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍል በሂደት ለሕዝብ/ለአንባቢያን የሚያቀርበው ያለ ጊዜ ገደብ ስለሆነ የሂደቶቹን እንቅስቃሴ በአግባቡና በወቅቱ እናቀርባለን። የሃሳብ ወይንም ኮሜንት መስጫ ቦታ ስላለን ተጠቀሙበት።

የተከበራችሁ ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተሰቦች አንደምን ሰነበታችሁ።
አንደምታስታውሱት ባለፈው በ9/23/10 ከቤተክርስቲአናችን አባላት መካከል በአቶ ሰይፉ ይገዙ የሚመራ የሽምግልና ኮሚቴ ጋር ኮሚቴአችን ተሰብስቦ አንደነበር በዚሁ ጦማር ላይ አስነብበናችሁ ነበር። አነሆ አሁን ደግሞ ባለፉት ሁለት ወራት የሽምግልናው ኮሚቴ አባላት የተወስኑ የሚካኤል አባላትና የሚካኤል የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት በየመስመራቸው ሽምግልናው ይሳካ ዘንድ ውይይቱን ቀጥለዋል ምንም አንኩዋን የቤተክርስቲያኑ ቦርድ አንካሳ ምክንያት አየደረደረ ቢገኝም ውይይቱ አንደቀጠለ ነው። በቅርቡም በሽምግልናው በኩል ያለው ሁኔታ በአጠቃላይ አናቅርብላችኋለን አስክውዚያው ቸር ይግጠመን።

ከሕዝብ ግንኙነት ክፍል